በፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባለሙ...

image description
image description
image description
image description
- Recent News   

በፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባለሙያዎች በኩል ከሪፎርም እና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ክትትልና ድጋፍ ተደረገ

የጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል ዓላማ ፈጻሚዎች እና የደጋፊ የስራ ሂደቶችን ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በመጡ ባለሙያዎች በዛሬው ዕለት ድጋፍ እና ክትትል ተደረገ፡፡
በክትትል እና ድጋፍ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የማዕከሉ የኢኮቱሪዝም ልማት ዘርፍ ም/ዳይሬክተር አቶ ሞገስ አባተ ሲሆኑ ይህ ክትትል እና ድጋፍ በቀጣይ ለምንሰራቸው ስራዎች መሳካት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖርውና ለሚደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን በማስተላለፍ ፕሮግራሙን አስጀምረዋል፡፡ 
በመቀጠል ክትትል እና ድጋፉን ከፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ቢሮ በመጡት ወ/ሮ መሰረት ወንደሜነህ እና አቶ ጌታቸር በላቸው ያከናወኑ ሲሆን ከማዕከሉ የአላማ ፈጻሚዎች እና ደጋፊ የስራ ክፍሎች የተለያዩ ማስረጃዎችን እና ሰነዶችን በመመልከት በቀጣይ መስተካከል ያለባቸውን ጉዳዮች በማንሳት ከማኔጅመንት አባላቱ ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
በመጨረሻም የማዕከሉ የምርምር ልማት ዘርፍ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ደባላ ብሩ ድጋፍ እና ክትትሉ ማዕከሉን በቀጣይ ለሚሰራቸው ስራዎች የሚያግዝ መሆኑን በመግለጽ ሃሳባቸውን በመስጠት የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡