በጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል የተግባር ተኮር ትምህር...

image description
image description
image description
- Recent News   

በጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል የተግባር ተኮር ትምህርት ለተማሪዎች ተሰጠ

ጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለመጡ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የተግባር ተኮር ትምህርት ሰጠ፡፡ ተማሪዎቹ ከአገሪ ቱሉ ፣ከምዕራፍ እና ከድልበር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጡ ሲሆን በተግባር የተደገፍ የብዝሀ-ሕይወት ትምህርት በማዕከሉ የብዝሀ-ህይወት ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዩሀንስ መላኩ ተሰጥቷል፡፡
በዚህም አበባ ያላቸው ዕፅዋት ከሌላቸው እንዴት ይለያሉ፣ መከለያ ቤት ጠቀሜታው፣ ስለበረሀማ ዕፅዋት ምንነት፣ ስለችግኝ ጣቢያ አገልግሎት የዕፅዋት ብዜትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ ሲሆን በተማሪዎቹ በኩል ለተነሱ ጥያቄዎችም ዳይሬክተሩ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡