የማዕከሉ የማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች የወንዞች ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች ላይ ልምድ ቀሰሙ
ጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል የማኔጅመንት አባላትና የሆርቲካልቸር ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ እና በየካ ክፍለ ከተማ መካከል ያከናወናቸውን የወንዝ ልማት ፕሮጀክት ላይ የልምድ ልውውጥ አደረጉ።
የዕፅዋት ማዕከሉ ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች አንዱ በሆነው የዕፅዋት ጥበቃ ፣እንክብካቤና የማሥዋብ ሥራ ላይ በተለይ በወንዞች ልማት ፕሮጀክት የታየው እጅግ አስደማሚ ከሆነው የአረንጓዴ ልማት ሥራ አፈፃፀም ላይ ማዕከሉ ትልቅ ልምድ ቀስሟል።
ማዕከሉ በቀጣይ በሚያከናውናቸው ተያያዥ ሥራዎች ያገኘውን ልምድ እንደሚጠቀም የሆርቲካልቸር ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መክብብ ማሞ ገልጸዋል ።