ማዕከሉ በአረንጓዴ ልማት ላይ ለተደራጁ ወጣቶች...

image description
- Recent News   

ማዕከሉ በአረንጓዴ ልማት ላይ ለተደራጁ ወጣቶች እና ሴቶች ስልጠና መስጠት ጀመረ

የጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 በአረንጓዴ ማስዋብ ሥራ ላይ በማህበር ለተደራጁ ወጣቶችና ሴቶች የአምስት ቀናት ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ በመክፈቻ ስንስርዓቱ ላይ የተገኙት የማዕከሉ የኢኮቱሪዝም ዘርፍ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሞገስ አባተ ስልጣኞቹን እንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኃላ ስልጠናው ለተሰማሩበት ዘርፍ ተጨማሪ አቅም ስለሚሆናቸው በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡ስልጠናውን ያዘጋጀውና ያስተባበረው የማዕከሉ የብዝሀህይወት ትምህርት ዳይሬክቶሬት ሲሆን ከሌሎች የሥራ ክፍሎችም የተውጣጡ ባለሙያዎች በአሰልጣኝነት ይሳተፋሉ፡፡ ስልጠናው የሚሰጠው የዕፅዋት እንክብካቤና ስለዕፅዋት አገራረዝ፣የዕፅዋት የማባዛት ሂደት፣የኮምፖስት ዝግጅት እና በመሬት አጠቃቀም ዙሪያ መሆኑ ታውቋል፡፡