ወርቃማው ሰኞ በጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል ተካሄደ

image description
- Recent News   

ወርቃማው ሰኞ በጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል ተካሄደ

የጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል አመራሮችና ሰራተኞች በወርቃማው ሰኞ ወርቃማ ልምዶችን በማካፈል ሳምንቱን በአዲስ መንፈስ እና በተነቃቃ መልኩ የተሰጠንን ኃላፊነት እንዴት መወጣት እንዳለብን በሚያሳይ ስኬት በሚል ርዕስ በቀረበ ሰነድ ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡
የዕለቱን አጀንዳ የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኢንጂነር ጉተማ ሞረዳ የከፈቱት ሲሆን በወርቃማው ሰኞ ሰራተኛው ከህይወት ተሞክሮ ፣ ከስራ ልምድ እና ከትምህርት የሚያገኘውን አስተማሪና አዝናኝ የሆኑ ልምዶችን ማካፈል ለተሻለ ስራ እንደሚያግዝ በመግለጽ ውይይቱን አስጀምረዋል፡፡
በመቀጠል የማዕከሉ አማካሪ በሆኑት አቶ ፋሩቅ ጀማል ”ስኬት” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ሰነድ ውስጥ ስኬት ማለት ምን ማለት ነው፤ አንድ ሰው ስኬታማ እንዲሆን የሚያስፈልጉት መሰረታዊ ብቃቶች ፤ የስኬት መርሆች፤ የስኬት ቁልፎች እና ስኬታማ እንዳንሆን ወደ ውድቀት የሚወስዱንን አቅጣጫዎች የሚያመለክት አስተማሪ ሰነድ ቀርቦ በማዕከሉ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎበታል፡፡