ወርቃማው ሰኞ በጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል

image description
- Recent News   

ወርቃማው ሰኞ በጉለሌ የዕፅዋት ማዕከል

ወርቃማው ሰኞ በማዕከሉ የሚገኙ አመራሮችና ሰራተኞች በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ሰራተኞችን ሊያስተምር ይችላል ተብለው በተመረጡ ርዕሶች ላይ ልምዶችን የሚለዋወጥበት መድረክ ነው፡፡

የዛሬው የወርቃማ ቀን ርዕስ ”ለሀገር ብልጽግና መትጋት” የሚል ሲሆን ሰነዱን የማዕከሉ አማካሪ የሆኑት አቶ ፋሩቅ ጀማል አቅርበዋል፡፡

በሰነዱ ውስጥ ሀገራዊ የሆኑ እና ወደ ግል ህይወት እና ወደ ሥራ ቦታችን አምጥተን ልንተገብራቸው የሚገቡ ሃሳቦች ተካተዋል፡፡ ከነዚህም መካከል ጊዜና ጉልበትን ሌሎችን ለመርዳት መጠቀም ፣ ህግና ስርዓትን ማከበር አካባቢን መንከባከብ ፣ መልካም ሃሳቦችን በነፃነት መግለጽ፣ ከተሰጠን ሃላፊነት በላይ መስራት፣ የሀገራችንን ታሪክ ጠንቅቀን ማወቅ ፣ ከመብት በፊት ግዴታችንን መወጣት እንዳለብን፤ የተለያዩ በጎ አድራጎት ስራ ላይ መሳተፍ ፤ እና የሀገር ፍቅር ሊኖረን እንደሚገባ ከሰነዱ እና ከህይወትና ከስራ ላይ ተሞክሯቸው ጭምር በማጣቀስ አቅርበዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ኑሬ ቀመር (የማዕከሉ አማካሪ) ሀገር ማለት ህይወት ማለት እንደሆነ እና የሀገርን ጠቀሜታ በጦርነት ምክንያት ችግር ውስጥ ከወደቁት ጎረቤት ሀገሮች መማር እንደምንችል በመግለጽ ሀገራችንን በየትኛውም መልኩ በተሰማራንበት የሙያ ዘርፍ በትጋት በመስራት የተጀመረውን ለውጥ ዳር ማድረስ እንዳለብን መልዕክታቸውን በማስተላለፍ የዕለቱን መድረክ ተጠናቋል፡፡