የማዕከሉ አራቱ ዓላማ ፈጻሚዎች የህዳር ወር የስ...

image description
- Recent News   

የማዕከሉ አራቱ ዓላማ ፈጻሚዎች የህዳር ወር የስራ አፈጻጸም እና በማዕከሉ ስለተካሄደውን ሁነት ሪፖርት ቀረበ

የጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል ዓላማ ፈጻሚዎች በህዳር ወር ያከናወኑትን ተግባራት እና በማዕከሉ ለሶስት ቀናት የቆየውን ሁነት በተመለከተ የማዕከሉ ጠቅላላ ካውንስል አባላት በተገኙበት  ሪፖርት ቀረበ፡፡  
የዓላማ ፈጻሚዎቹን የህዳር ወር ሪፖርት የማዕከሉ ዕቅድና በጀት ክትትል ግምገማ ዝግጅት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ምስክር ታዬ አቅርበዋል፡፡ 
በመቀጠል ከህዳር 27 - 29 2018 ዓ.ም የተዘጋጀውን ሁነት  የኢኮቱሪዝም ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳንኤል አማረ ያቀረቡ ሲሆን በሁነቱም ላይ  የተራራ መውጣት፤ የዱር አዳር ፕሮግራም፤ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ፤ የተለያዩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም የፓናል ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ጉተማ ሞረዳ ባደረጉት የማጠቃለያ ሃሳብ በቀረበው የህዳር ወር ሪፖርት ላይ በሰጡት ሃሳብና አቅጣጫ መሰረት ለቀጣይ መስተካከል ያለባቸውን ነጥቦች በማንሳት ከክፍሎቹ ኃላፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ሁነቱን በተመለከተ ማዕከሉን ለማህበረሰቡ ከማስተዋወቅ አኳያ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳደረገ በመግለጽ ይህንን ሁነት እንዲሳካ ላደረጉ ለኢኮቱሪዝም ክፍል ባለሙያዎች በሙሉ ከፍተኛ ምስጋናቸውን በማቅረብ የዕለቱን አጀንዳ ተጠናቋል፡፡